በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተደገፈ የቁጠባ፣ የብድር እና የፋይናንስ መፍትሄዎችን ለአባላቶቻችን እናቀርባለን።
አባይ እና ጣና ኃ.የተ.መ.ቁ.ብ/ኅብረት ማህበር የአባላትን የኢኮኖሚ አቅም ለማሳደግ የተቋቋመ ዘመናዊ የህብረት ስራ ማህበር ነው።
የቤት ግንባታ፣ የመኪና ግዢ፣ የግል ልማት እና ሌሎች ፋይናንስ ፍላጎቶችን በተመጣጣኝ የብድር አገልግሎት እንዲያሳኩ እንረዳለን።
የተቋሙ ዓላማ፣ ግብ፣ ራዕይ፣ ተልዕኮ እና እሴቶች
የህብረተሰቡን የፋይናንስ አቅም በማሳደግ የአባላትን የኢኮኖሚና የማህበራዊ ኑሮ ማሻሻል ነው።
የህብረተሰቡን ተቀማጭ በማሰባሰብ የፋይናንስ አቅም ማሳደግና የአባላትን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ።
በ2022 ዓ.ም. የአባላትን የገንዘብ አቅም በማሳደግ በአገር አቀፍ ደረጃ ተመራጭ የቁጠባና ብድር ተቋም ሆኖ መታየት።
ለአባላት አስተማማኝ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የፋይናንስ አገልግሎት በመስጠት፣ የቁጠባ ባህልን በማጎልበትና የኢኮኖሚ እድገትን በመደገፍ የአባላትን ተጠቃሚነት ማሳደግ።